በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ወረዳ 09 አስተዳደር ስር የሚገኘው ትምህርት ቤቱ ተማሪዎች በትምህርት ብቻ ሳይገደቡ በተግባር የሚማሩ ክህሎቶችን እንዲያገኙ የተለያዩ የእደ ጥበብ ስራዎች ላይ ስልጠና በመስጠት ላይ ይገኛል።
በዚህም ተማሪዎች የስራ ባህልን እንዲያጎለብቱ ፣ የፈጠራ ችሎታቸውን ለማጠናከር እና ወደፊት የሚያገለግላቸውን ተግባራዊ ክህሎት ለማግኘት እድል እያገኙ ያግዛቸዋል።
የእደ ጥበብ ስልጠናው ከትምህርት ጥራት ማሻሻል ጋር ተያይዞ ተማሪዎች እውቀታቸውን በተግባር እንዲያጠናክሩ የሚያግዝ መሆኑ ከክፍለ ከተማው ያገኘነው መረጃ የሚያሳይ ሲሆን ይህም ተማሪዎች በመማር ሂደታቸው ውስጥ ተሳትፎአቸውን እንዲጨምሩ እና የራሳቸውን ፈጠራ አቅም እንዲያሳድጉ እንደሚያግዝ ተመላክቷል።
በተጨማሪም ይህ አሰራር ተማሪዎች ከህፃናትነታቸው ጀምሮ የስራ ክብርን እንዲገነዘቡ እና በፈጠራ ስራዎች ላይ እንዲሳተፉ የሚያበረታታ መሆኑ ተጠቁሟል።
ትምህርት ቤቶች ውስጥ የትምህርት ጥራትን ለማሻሻል እና ተማሪዎችን በተግባር የተደገፈ እውቀት እንዲያገኙ የሚያግዙ መርሀ ግብሮች በተከታታይ እየተተገበሩ የሚገኙ ሲሆን መሰል ተግባራት በፈጠራ እና በሙያ ክህሎት የተዘጋጁ ዜጎች እንዲፈሩ የሚያግዝ ነው።
.