በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሙሉ በሙሉ በበይነ መረብ በመሰጠት ላይ በሚገኘው የ 2017 ትምህርት ዘመን የመጀመሪያው ዙር የማህበራዊ ሳይንስ የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከ12ሺ በላይ ተፈታኞች ፈተናውን በመውሰድ ላይ ይገኛሉ::
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ከምክትል ቢሮ ኃላፊ ከአቶ ዲናኦል ጫላ ፣ ከኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ፕሬዝዳንት ዶክተር ብርሀነመስቀል ጠና እና ከዩኒቨርስቲው አመራሮች ጋር በመሆን በኮተቤ ትምህርት ዩኒቨርሲቲ መፈተኛ ጣቢያ ተገኝተው ለ3ኛ ቀን በመሰጠት ላይ የሚገኘውን የማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት ዘርፍ ፈተና አሰጣጥ ሂደትን በመመልከት ተማሪዎችን አበረታተዋል።
.