የተማሪዎች ውጤትና ስነምግባር በላቀ ሁኔታ እንዲሻሻል ወላጆች ኃላፊነታቸውን ሊወጡ እንደሚገባ የልደታ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት በተማሪዎች ውጤት እና ስነምግባር ማሻሻል ዙሪያ ከተማሪ ወላጆች ጋር ባደረገው ውይይት ላይ የተገለጸ ሲሆን በመድረኩ የልደታ ክፍለ ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ በላይነሽ ሞሲሳ ፣ የኢትዮጵያና የአዲስ አበባ የተ.ወ.ማ ፕሬዝዳንት አቶ ሃሰን ሺፋ እና የትምህርት ጽ/ቤት የስራ አስተባባሪ አቶ አቡበከር አህመድ ፣ የክ/ከተማ ፣ የወረዳ እና የት/ቤት የተ.ወ.ማ አባላት ተገኝተዋል።
የልደታ ክ/ከተማ ትምህርት ጽ/ቤት ኃላፊ ወ/ሮ በላይነሽ ሞሲሳ የተማሪዎች ውጤት እና ስነምግባር በላቀ ሁኔታ እንዲሻሻል ወላጆች ኃላፊነታቸው መወጣት እንዳለባቸው ገልጸው ተማሪዎች ተገቢነትና ጥራት ያለው የትምህርት አገልግሎት እንዲያገኙ፣ ት/ቤቶች በግብዓት እንዲሟሉ እንዲሁም በት/ቤቶች ሠላማዊ የመማር ማስተማር ስራ በአግባቡ እንዲካሄድ ወላጆች እና የተማሪ ወላጅ ማህበር [ተ.ወ.ማ] የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ማበርከት ይኖርባቸዋል ብለዋል።
የኢትዮጵያና የአዲስ አበባ የተ.ወ.ማ ፕሬዚዳንት አቶ ሃሰን ሺፋ በበኩላቸው ወላጆች ት/ቤቶችን በባለቤትነት፣ በተጠያቂነትና በተቆርቋሪነት መምራት እንደሚጠበቅባቸው ገልጸው በየት/ቤቱ ያሉ የተ.ወ.ማ አባላት በት/ቤት ግቢ ውስጥ በመገኘት አርፋጅ ተማሪዎችን የመምከር ፣ በሰልፍ ስነስርዓት የማስተባበር፣ የተማሪዎች ምገባን የማስተባበር እንዲሁም በጸጥታ ኮሚቴ ውስጥ በቀጥታ በመሳተፍ በት/ቤቶች ሠላማዊ የመማር ማስተማር ስራ እንዲካሄድ የማድረግ ኃላፊነትን መወጣት ያስፈልጋል ብለዋል።
የትምህርት ጽ/ቤት የስራ አስተባባሪ አቶ አቡበከር አህመድ የተማሪዎች ውጤት እና ስነምግባር በላቀ ሁኔታ እንዲሻሻል የተማሪ ወላጅ ማህበር ሚናን አቅርበው ውይይት ተካሂዳል፡፡
.