About የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጠቅላላ ካውንስል የሁለት ሳምንት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ግምገማ አካሂዷል ::

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ጠቅላላ ካውንስል የሁለት ሳምንት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ላይ ግምገማ አካሂዷል ::

14th June, 2025

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የሚዲያ ይዘት ማበልፀግና ስርጭት ዳይሬክቶሬት እና የልዩ ፍላጎት አካቶ ትምህርት ትግበራ ዝግጅትና የጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ትግበራ ዳይሬክቶሬት የ2017 በጀት ዓመት የግንቦት ወር 2 ሳምንታት እቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ለቢሮው ጠቅላላ ካውንስል አቅርበው ግምገማ ተካሂዷል::

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ፅ/ቤት ኃላፊ አቶ ሲሳይ እንዳለ የስራ አፈፃፀም ሪፖርቶችን በየጊዜው መገምገም በጥንካሬ የሰራነውን ለማስቀጠልና እጥረቶች ላይ በአፋጣኝ እርማት ለመውሰድ እንደሚያስችል ገልፀዋል :: አያይዘውም በዚህ መድረክ የሚቀርቡ ሪፖርቶች የሪፎርም ሥራዎች ላይ የበለጠ ትኩረት ሰጥተው እንዲቀርቡ አሳስበዋል ::

የቢሮ ኃላፊ አማካሪ ወ/ሮ አበበች ነጋሽ በበኩላቸው  የቀረቡ ሪፖርቶች ሥራዎቻችን በተቀመጠላቸው ወቅት በጥራት ለማጠናቀቅ የተሄደበትን ርቀት የሚያሳይ መሆኑን ተናግረዋል :: ሪፖርቶች ሲቀርቡ  የሪፖርት መላኪያ ቢጋሩን በተከተለ መልኩ  እንዲሆን እና የአቻ ፎረም መወያያ አጀንዳዎች ላይ ትኩረት በማድረግ ሊሆን ይገባል ብለዋል::

በዳይሬክቶሬቶቹ የሚሰጡ ዋናዋና አገልግሎቶች ውስጥ በ2ሳምንት የተከናወኑ አበይት ተግባራት ሪፖርት የሚዲያ ይዘት ማበልፀግና ስርጭት ዳይሬክተር ወ /ሮ የውብዳር አያሌው እና የልዩ ፍላጎት አካቶ ትምህርት ትግበራ ዝግጅትና የጎልማሶች መሰረታዊ ትምህርት ትግበራ ዳይሬክተር አቶ ገመቺስ ፈቃዱ አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል ::

.

Copyright © All rights reserved.