Home አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 በሚገኘው ብሔራዊ ቤተመንግስት አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምልከታ ተካሄደ።

አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 6 በሚገኘው ብሔራዊ ቤተመንግስት አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምልከታ ተካሄደ።

03rd January, 2026

በምልከታው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱን ጨምሮ የአራዳ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ ወንድሙ ኡመር እና የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ዱጋሳ ፍቃዱ ተገኝተዋል።

ብሔራዊ ቤተመንግስት አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ምድረ ግቢው ጠባብ ከመሆኑ የተነሳ የተማሪዎች መማሪያ ክፍል ጥበትና የአስተዳደር ስራዎችን ለመስራት የሚያስችል የቢሮ እጥረት በመኖሩ ከትምህርት ቤቱ ማህበረሰብና ከወላጆች የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመቅረፍ እንዲቻል በትምህርት ቤቱ ምልከታ መደረጉን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዶክተር ዘላለም ሙላቱ አስታውቀዋል።

ኃላፊው አያይዘውም በቀጣይ የትምህርት ቤቱን ቅጥር ግቢ ለተማሪዎች ምቹ የመማሪያ ስፍራ እንዲሆን የማስዋብና የአስተዳደር ስራዎችን መስራት የሚያስችሉ ተጨማሪ ቢሮዎች ተገንብተው ከህብረተሰቡ የሚነሱ የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ምላሽ እንዲያገኙ ለክፍለከተማው አስተዳደር አቅጣጫ መሰጠቱን አመላክተዋል።

.

Copyright © All rights reserved.