About የመምህራን እና የትምህርት አመራር ልማት ዳይሬክየመምህራን እና የትምህርት አመራር ልማት ዳይሬክቶሬት በ2017 ዓ.ም አፈጻጸም እና በ2018 ዓ.ም እቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄደ።

የመምህራን እና የትምህርት አመራር ልማት ዳይሬክየመምህራን እና የትምህርት አመራር ልማት ዳይሬክቶሬት በ2017 ዓ.ም አፈጻጸም እና በ2018 ዓ.ም እቅድ ዙሪያ ውይይት አካሄደ።

05th July, 2025

በውይይቱ የክፍለከተማ የመምህራን እና የትምህርት አመራር ልማት ቡድን መሪዎች እንዲሁም የዳይሬክቶሬቱ ባለሙያዎች የተሳተፉ ሲሆን በመርሀግብሩ የ4ኛ ሩብ አመት አፈጻጸምን መሰረት ያደረገ የድጋፍና ክትትል ግብረ መልስ በቢሮ የመምህራን ልማት ባለሙያ በወይዘሮ ፍሬሕይወት አስፋ ቀርቦ ውይይት ተካሂዷል።

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ የመምህራን እና የትምህርት አመራር ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ አበራ ስራ ክፍሉ በየሩብ አመቱ በዘርፉ የተከናወኑ ተግባራትን ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በጋራ በመሆን ሲገመግም መቆየቱን ገልጸው የዛሬው ውይይት በበጀት አመቱ የተከናወኑ ተግባራትን በመገምገም በ2018ዓ.ም የተሻለ ስራ ለመስራት የሚያስችል  መሆኑን  አስታውቀዋል።

ዳይሬክተሩ አያይዘውም ስራ ክፍሉ የ4ኛ ሩብ አመት አፈጻጸምን መሰረት ያደረገ ድጋፍና  ክትትል ማድረጉን ገልጸው የድጋፍና ክትትል ግብረመልሱን የጋራ በማድረግ በቀጣይ የተሻለ ስራ የሚሰራ መሆኑን አመላክተዋል።

በመርሀግብሩ በዘርፉ በ90 ቀናት በሚከናወኑ ተግባራት ዙሪያ ውይይት ከመካሄዱ ባሻገር በ2017 ዓ.ም የመምህራን ኦዲት ሪፖርትን የጋራ የማድረግና በ2018 ዓ.ም የመምህራን ፍላጎት ዙሪያ ውይይት ተደርጎ ቀጣይ አቅጣጫ ተቀምጧል።

.

Copyright © All rights reserved.